Jump to content

ኪንዳቱ

ከውክፔዲያ

ኪንዳቱ ከ1901 እስከ 1878 ዓክልበ. አካባቢ (ኡልትራ አጭር አቆጣጠር) የኤላም ስሜናዊ ጐረቤት አገር ሲማሽኪ ንጉሥና በኤላም የሲማሽኪ ሥርወ መንግሥት ስድስተኛው ንጉሥ ነበር።

የርሱን እና የሲማሽኪን ነገሥታት ታን-ሩሁራተር፣ ኢዳዱና ኢማዙ ሕልውና የሚያረጋግጡ ሰነዶች ከዑር-፫ አሉ። መጨረሻ ሁለቱ የኪንዳቱ ልጆች ተባሉ።[1]

በኪንዳቱ ዘመን ሲማሽኪ ለታላቁ የዑር-፫ መንግሥት ተገዥ ነበር።[2] ከኤላም ክፍሎች ለምሳሌ የሱሳን ሸለቆ በቀጥታ ከሱመራውያን ግዛት በታች ቆሙ። በ1879 ዓክልበ. ግን ኪንዳቱ የኤላማውያንና የሲማሽኪን ኃያላት ለማዋሀድ የዑርንም ንጉሥ ኢቢ-ሲን በጭራሽ ለማሸንፍ ቻለ። ኢቢ-ሲን እንደ እስረኛ ወደ አንሻን ተጎትቶ ከታሪኩ ጠፋ። ዑር ተፈረሰ።

በኪንዳቱና በኢሽቢ-ኤራ አሞራውያን መካከል የነበረው መተባበር በመጀመርያ ምናልባት በጋራ ጠላት በዑር-፫ መንግሥት ላይ ቢሆንም፣ ለእሽቢ-ኤራ ለኢሲን መጀመርያው ሥርወ መንግሥት መሥራች ክብር በኋላ የተጻፈ አንድ መዝሙር ኪንዳቱን ከመስጴጦምያ እንዳባረረው ይጠቅሳል። የኤላማውያን-ሲማሽኪ አስተዳደር እንግዲህ ለአጭር ጊዜ ነበር።

ልጁ ኢዳዱ እንደ ተከተለው ይሆናል።

  1. ^ Arsacids and Sassanians. M.Rahim Shayegan 2011 ISBN 978-0-521-76641-8
  2. ^ The Oxford handbook of Iranian history. Touraj Daryaee. ISBN 978-0-19-973215-9