Jump to content

ዘረኝነት

ከውክፔዲያ

ዘረኝነት አንድ የህዝብ ወገን በውጫዊ ማንነቱ ብቻ የሚገለጥ ከሌሎች የሚበልጥበት ባህርይ አለው ብሎ የሚያምን አመለካከት ነው። ይህም ሌላውን ወገን በንቀትና በማጣጣል የሚያርቅ፣ የሚቃረንና ብሎም እስከ ማጥቃት (ማጥፋት) የሚዘልቅ ነው። አሁን ያለው ዘረኝነት የተመሠረተው በሰዎች ውጫዊ (ሥነ ሕይወታዊ) ልዩነት ላይ ነው። ለምሳሌ የቀለም ልዩነትን የዚህ አመለካከት አራማጆች በዋናነት ይጠቀሙበታል። ዘረኛው በማህበረ ሰብ ውስጥ በሁሉም መስክ የአንዱን ዘር ተፈጥሮአዊ የበላይነት በሌላው የበታችነት ለማረጋገጥ ተግቶ ይሠራል።